Community empowerment (SBCC) on LLINS utilization at SWER-Tercha

የወባ ማስወገድና ህብረተሰብ ጤና ልማት ማህበር በደቡብ ምዕራብ ኢትዮዽያ ክልል በተርጫ ከተማና በተርጫ ዙሪያ ወረዳ የወባ መከላያ አጎበር አጠቃቀምን ለማሻሻል የማህበረሰብ ንቅናቄና  የቅስቀሳ ስራ  ከፌዴራል የጤና ሚኒስቴርና ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮዽያ ክልል ጤና ቢሮ ጋር በመተባባር ከ08/01/2018 ጀምሮ ለ4 ተከታታይ ቀናት አካሂዷል፡፡ የንቅናቄዉን ስራ ዉጤታማ ለማድረግ ከባለድርሻ አካላት ጋር ማለትም የክልሉ ጤና ቢሮ፣ የዳዉሮ ዞን ጤና መምሪያ፣ የማህበሩ  እንድሁ የተርጫ  ከተማ አሰተዳደር ጤና ጽ/ቤት  ተወካዮች ባሉበት የምክክር ሰብሰባ በተርጫ ከተማ አስተዳደር ጤና ጽ/ቤት  ተካሂዷል፡፡ በወቅቱ በወረደዉ ከ14,000 በላይ አጎበር ከ6,000 በላይ አባወራ ተሰራጭቷል:: በተጨማሪ 39,250 አጎበር በተርጫ ዙሪያ ወረዳ ለማሰራጨት ዝግጅት አጠናቀዋል።፡፡

በቅስቀሳ ዘመቻዉ ህብረተሰቡ አጎበር በአግባቡ እንዲጠቀም፣ የወባ ትንኝ መራቢያ ቦታዎችን እንዲያፋስስ፣ ቤቶችን እነዲያስረጭ ፣ የወባ ህመም ምልክቶች ሲታዩ ወድያዉ በአቅራቢያቸዉ ወደሚገኝ የጤና ድርጅት ሄደዉ እንድታከሙ  በድምሩ በ17 ቀበሌዎች በገበያ ፣በህዝብ መሰብሰቢያ ቦታዎችና በመንገድ ዳር መልእክቶች ተላልፈዋል፡፡ በንቅናቄ ዘመቻዉ በድምሩ ለ80,000 በላይ ህዝብ የወባ መከላከል መልእክቶች ተደራሽ ሆነዋል፡፡

  ወባን በጋራ እናስወግድ!!

Scroll to Top